ስለ መነኩሴ

የመነኩሴ ጽንስ ሃሳብ በጥቂቱ

መነኩሴ ጠቅላላ ህይወቱን ለእግዚአብሄር የሰጠ ፡ በፈቃደኝነት እራሱን ደሃ በማድረግ ለምንም ዓለማዊ  ኑሮ ፡ ገንዘብ ፡ ምቾትና የግል ጥቅም ሳይደለል ለዓለም ሁሉ ሰላም በመጸለይ ለበጎ ስራ ቃል ኪዳን የገባ በሁሉም የታመነ የቤተክርስቲያን ቅን አገልጋይ ማለት ነው፡፡  የመለኩሴም ጽንሰ ሃሳብ የተወለደው የነዚህን መነኩሴዎች የበጎ ስራ ጽናትና ራዕይ በመከተል በቀና መንፈስ ህብረተሰብን በማነቃቃት፤ ከቤተክርስቲያን ጎን ተሰልፎ ያለውን ዕውቀትና ገንዘብ በማካፈል ጥንታዊና ታሪካዊ ቤተክርስቲያናችንን ለመጠበቅና ለማሳደግና በቅድስት አገር ኢየሩሳሌም ያሉንን ገዳማት ህጋዊ መብት አስከብሮ ለመርዳትና ለሰው ልጆች ህይወት በሚቻለው ሁሉ ለመርዳት ነው፡፡

A Bit of Background

Menekuse is the Amharic word for a monk.  A Menekuse is an individual who is totally dedicated to God, takes the vows of poverty, chastity and obedience.  They serve the church with dedication, work for the salvation of the world, and give their lives to charity work.  The vision of Menekuse is born out of the lives of these dedicated Menekuses.  Our vision is to empower communities by partnering churches, imparting vision to the next generation, and bring together people to preserve the Ethiopian churches and support our monasteries in Jerusalem.

በፋና የእርዳታ ተግባራት 

1.  ቤተ ክርስቲያናትን ማጠናከር 

የኢኦትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ብዙ ፈተና ቢያጋጥማትም እስከ ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ማብቂያ 1966 ድረስ የነበሩት ነገስታት ለቤተክርስቲያን ታላቅ አክብሮት ስለነበራቸው የጠፉት እየተገነቡ በጥሩ ቀጥላለች ። በ1966  ስልጣን የያዘው የደርግ መንግስት ሃይማኖት ጠል ፖሊሲ ስለሚከተል  ያለአግባብ  ህብትዋን  ወርሶ ፓትርያርክዋን ገድሎ አስተዳደርዋ እንዲዳከም የጀመረው መቅሰፍት እስከ አሁንም እየተባባሰ ቀጥሎ ህልውናዋን እየፈተናት ቢሆንም ፣ ዛሬ ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን 50 ሚሊዮን የሚገመቱ አማንያን ፣ በርካታ የሃይማኖት አባቶች  ስባኪ መምህራን ፣ በተለያየ  ዘመናዊው የምዕራባውያን ትምህርት እስከ ዶክትሬትና ፍልስፍና ቢሰለጥኑም በሃይማኖታዊ ትምህርትም እስከ ዶክትሬት  በመማር ሃይማኖትን የሚታደጉ፣  በአንገታቸው ማህተባቸውን እስከ ሞት አስረው ጸንተው  የሚቆሙ  ፣  አጽዋማትን አምነው የሚጾሙ ፣  ስርዓተ ቅዳሴን ፣ ማህሌቱን ዝማሬውን  የሚያንቆረቁሩ ፣ ለጉባኤና ለታቦት ንግስ አገር አቋርጠው የሚጓዙ ፣  ሃይማኖት የሚሰራጩባቸው ሬዲዮና ቴሊቪዥኖች ። የተደራጉ ማህበሮች ፣  የሰንበት ትምህርት ቤቶች ፣ በገንዘብና በስልጣንም ከፍተኛ ቦታ ያላቸው አማኞች ያሉበት  ዘመን ከመሆኑም ባሻገር  በደረሰባቸው በደል ኦርቶዶክሳውያን በመላው ዓለም በመበተናቸው  ባሉበት ሁሉ ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን  በዓለም ከተሞች  እያበበች ፣ የሌሎች ሃገሮች  ዜጋዎችም  እምነቱን  እየተቀበሉ  ጋብቻቸውን በቅዱስ ቁርባን የሚፈጽሙባት ሆናለች ።

ፋና የብርሃን ተግባሮች 

1. የእምነታችንን ቁልፍ የሆነውን የግዕዝ ቋንቋን ማወቅ


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ የአምልኮት ስርዐት በካህናትና በሊቃውንቱ ሲፈስ መንፈስን በመመሰጥ የሰው ልጅን ከአምላክ ጋር የሚያገናኝና ለአምላካችን ምስጋና በቂ ጊዜን የሚሰጥ በመሆኑ እንከን አይወጣለትም፡፡  አብዛኛው የቅዳሴያችን ስርዐት፡ ማህሌቱና ወረብ  የሚከናወነው በግዕዝ በመሆኑ ያንን የመሰለ መሳጭ አገልግሎት ሁላችንም ምዕመናን ተሳታፊ እንዳንሆንና እንዲሁም ብዙ ጥልቅ ምርምርና ዕውቀትን ያካተቱት  በግዕዝ የተጻፉ መጽሁፎቻችንን እንዳናነብ አግዶን ይገኛል፡፡ የዕውቀት ምንጭ መሆኑን ያወቁት  የውጭው ዓለም ግን ከኛው ተምረው በታላላቅ ዩኒቨርስቲያቸው እነሱው ግዕዝን ሲያስተምሩን እኛ ለመምህርነት እንኩዋን የማንበቃ ሆነናል። በተጨማሪም  እያሰረቁ የወስዷቸውን ብርቅ የእውቀት ማህደር በብራና የተጻፉ መጽሃፍቶቻችንን ከመጠቀማቸውም በላይ ሌላ ሊወስደው በማይችል ጥብቅ ቁጥጥር እያስጠበቁ ሲገለገሉበት ፣ እኛ ግን የበይ ተመልካች ሆንናል፡፡ይህንን ማነቆ ፈትተን ብርሃንኑ እኛም እንድናይ፡
ምዕመናን ከልብ ቆርጠን በመነሳት ግዕዝ መስማትና በግዕዝ የተጻፉ መጽሃፎችን ለማንበብና ለማወቅ መትጋት
ብዙ የግዕዝ ሊቃውንትና መምህራን ስላሉን ሁሉም በሚችሉት ትምህርቱን እንዲያስተምሩን ጥረት ማድረግ
ብዙ የቴክኖሎጂ እውቀት ባለሙያዎች ስላሉን  ግዕዝን በቀላሉ ለማስተማርና ለማዳረስ ከግዕዝ ሊቃውንቶቻችን ጋር በመተባበር የግዕዝ ማስተማሪያ /application/ ማዘጋጀት
የተዘጋጁት በስልክ ፣ በድህረ ገጽና ሌሎችም አመቺ ዘዴዎች ተጠቅሞ ኦርቶዶክሳውያን ሁሉ ግዕዝ አዋቂ ማድረግ

There is a lot that happens around the world we cannot control. We cannot stop earthquakes, we cannot prevent droughts, and we cannot prevent all conflict, but when we know where the hungry, the homeless and the sick exist, then we can help.

- Jan Schakowsky 

0

Feeded Homeless

0

build Shelters

$0

Money Donated

Our current Project

 

New Shelter at the Brooklyn Bridge

Lorem ipsum dolor sit amet, consetetur sadipscing elitr, sed diam nonumy eirmod tempor invidunt ut labore et dolore magna aliquyam erat, sed diam voluptua. At vero eos et accusam et justo duo dolores et ea rebum.

$56.000  - Already donated

65%